Skip to content 
Location
Arada Subcity, woreda 06 Addis Ababa, Ethiopia
Date
ሰኞ, 17 ግንቦት 2018 1:27 ከሰዓት
Last updated
May 25, 2026 13:27
Weather
addis ababa: ☀️ +27°C
ዜና

የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል

15 ግንቦት 2018

የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል
የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል
በዛሬ እለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን እና 18 ሱቆችና 18 ሼዶችን ያካተተ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት አስጀምረናል ።
ከተማችን ለሁሉም የምትመች የጋራ ቤታችን ናት ልማታችንም አካታች ነው። ባለፈው ስርዓት ውስጥ አርሶ አደሩ የሚገፋበት መሬቱ ብቻ ተፈልጎ የሚዘነጋበት በመሆኑ ለለውጡ መምጣት ገፊ ምክንያት ሆኗል።
አርሶ አደሩ በሁሉም የከተማ ልማት ዉስጥ አካተን አብሮ እንዲለማ እና ተጠቃሚነቱ እንረጋገጥ ከማድረግ ባሻገር ለልማት ሲነሳ ተገቢውን ካሳ ከማግኘት ባለፈ ከልማቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ከዚህን በፊት በአቃቂ ቂሊቲ ክፍለ ከተማ 14ሺ ሄክታር የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ልህቀት ማዕከልን የገነባን ሲሆን ዛሬ በለሚ ኩራ የመረቅነውም የዚሁ አካል ነው።
እነዚህን መሰል ማዕከላት በሌላ በኩል የከተማው ነዋሪ የሚያጋጥመውን የዋጋ ንረት ለመከላከል እና በተመጣጣኝ ዋጋ የግብርና ምርቶችን ለማቅረብ የሚያስችል ነው ይህን መሰሉ አሰራር በጋራ ማደግን ተባብሮ መበልጸግን የሚያሳድግ ነው።
ይህንን ስራ በማቀድ፣ በማስተባበር ውጤታማ ላደረጉ ሁሉ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ