የስራ ቅጥር ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ለአዲስ መሶብ ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት መ/ቤት በተለያዩ የስራ መደቦች ተፈላጊውን የስራ ችሎታ እና ልምድ የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል።
ፍላጎት ያላችሁ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ ሰባት ተከታታይ ቀናት በኦንላይን መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን።
ማሳሰቢያ፦
- ምዝገባ በኦንላይን ብቻ ይካሄዳል፤ በአካል መመዝገብ አይፈቀድም።
- ባለ16 ዲጂታል የናሽናል አይዲ ቁጥር (FAN / FCN) መኖር አለበት።
- የመጀመሪያ ዲግሪ ለሚጠየቁ መደቦች የአገር አቀፍ ፈተና ማረጋገጫ ያስፈልጋል።
- GPA፦ ለወንዶች 3.5 እና ከዚያ በላይ፣ ለሴቶች 3.0 እና ከዚያ በላይ።
- የዲፕሎማ/ሌቭል ተመራቂዎች COC ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ከ2015 ጀምሮ የተመረቁ መሆን አለባቸው።
ምዝገባ ለማድረግ ይህን ድረ-ገጽ ይክፈቱ
https://aacapsjobs.gov.et